top of page

7ቱ መመሪያዎች

ለመልካም ሕብረት

“ከክርስቶስ ጋር ካላችሁ አንድነት የተነሣ የትኛውም መበረታታት፣ ከፍቅር የሆነ መጽናናት፣ የመንፈስ ኅብረት፣ ምሕረትና ርኅራኄ ካላችሁ፣ በአንድ ሐሳብ፣ በአንድ ፍቅር፣ በአንድ መንፈስና በአንድ ዐላማ በመሆን፣ ደስታዬን ፍጹም አድርጉልኝ። ሌሎች ከእናንተ እንደሚሻሉ በትሕትና ቊጠሩ እንጂ፣ በራስ ወዳድነት ምኞት ወይም ከንቱ ውዳሴ ለማግኘት አንዳች አታድርጉ። እያንዳንዳችሁ ሌሎችን የሚጠቅመ ውንም እንጂ፣ ራሳችሁን የሚጠቅመውን ብቻ አትመልከቱ።” (ፊልጵስዩስ 2፥1-4)

  1. ፍቅር - ፍቅር ከእኔነት ሕይወት ይገላግለናል። በፍቅር ውስጥ ራስ ወዳድነት ሥፍራ የለውም።

    • “አዲስ ትእዛዝ እሰጣችኋለሁ፤ ይኸውም እርስ በርሳችሁ እንድትዋደዱ ነው፤ እንግዲህ እኔ እንደ ወደድኋችሁ እናንተም እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ። እርስ በርሳችሁ ብት ዋደዱ፣ ሰዎች ሁሉ የእኔ ደቀ መዛሙርት እንደሆናችሁ በዚህ ያውቃሉ።” (ዩሐንስ 13፥34-35)

  2. ማበረታታት - “እንደ አስፈላጊነቱ ሌሎችን የሚያንጽና ሰሚዎችን የሚጠቅም ቃል እንጂ የማይረባ ቃል ከአፋችሁ አይውጣ።” (ኤፌሶን 4፥29)

    • ለማነጽ እንጂ ለመፍረድ አልተጠራንም።

    • አዎንታዊ ገጽታው የጎላ ግንኙነት ያስፈልገናል።

    • ግሳጼያችን በየውሃት መንፈስ ሊታጀብ ይገባል።

    • “ወንድሞች ሆይ፤ አንድ ሰው በኀጢአት ውስጥ ገብቶ ቢገኝ፣ መንፈሳውያን የሆናችሁ እናንተ በገርነት ልትመልሱት ይገባል።” (ገላትያ 6፥1)

    • “እርስ በርሳችሁ ተመካከሩ አንዱም አንዱም ሌላውን ያንጸው።” (1ኛ ተሰሎንቄ 5፥11)

  3. መከባበር - “በወንድማማች መዋደድ እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ፤ እርስ በርሳችሁ ተከባበሩ” (ሮሜ 12፥10)

    • “ሁሉን አክብሩ” (1ኛ ጴጥሮስ 2፥17)

  4. ኃላፊነትን መውሰድ - “አንተ ግብዝ፤ በመጀመሪያ በዐይንህ ውስጥ የተጋደመውን ግንድ አውጣ፤ ከዚያ በኋላ በወንድምህ ዐይን ውስጥ ያለውን ጒድፍ ለማውጣት አጥርተህ ታያለህ።” (ሉቃስ 6፥42)

    • ሌላውን ለመገሰጽ ኃላፊነት ልንወስድ እንደሚገባን ሁሉ፥ እኛም ለገዛ ስኅተቶቻችን ኃላፊነት ለመውሰድ የበሰልን ሆነን መገኘት ይጠበቅብናል።

  5. ራስን መግዛት - “መራርነትን ሁሉ፣ ቍጣና ንዴትን፣ ጭቅጭቅና ስድብን ከማንኛውም ክፋት ጋር ከእናንተ ዘንድ አስወግዱ።” (ኤፌሶን 4፥31)

  6. ይቅርታ - “እግዚአብሔር በክርስቶስ ይቅር እንዳላችሁ፣ እናንተም ይቅር ተባባሉ፤ እርስ በርሳችሁ ቸሮችና ርኅሩኆች ሁኑ።” (ኤፌሶን 4፥32)

  7. ጸሎት - “ስለዚህ ኀጢአታችሁን እርስ በርሳችሁ ተናዘዙ፤ ትፈወሱም ዘንድ አንዱ ለሌላው ይጸልይ። የጻድቅ ሰው ጸሎት ኀይል አለው፤ ታላቅ ነገርም ያደርጋል።” (ያዕቆብ 5፥16)

    • “ወዳጅህን ውደድ፤ ጠላትህን ጥላ’ እንደ ተባለ ሰምታችኋል። እኔ ግን ጠላቶቻችሁን ውደዱ ለሚያሳድዷችሁም ጸልዩ እላችኋለሁ።” (ማቴዎስ 5፥43-44)

ጸጋ ከእርስዎ ጋር ይሁን!

ፓስተር መስፍን ማሞ

bottom of page